avatar
Ethiopian News Agency
@EthiopianNewsA
09.04.2026 12:29
የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የቡሩንዲ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ኢትዮጵያና ቡሩንዲ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው።

ሁለቱ ሀገራት የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን በማቋቋም በተለያዩ መስኮች ትብብራቸውን በማጠናከር ላይ ይገኛሉ።

የቡሩንዲ ፕሬዝዳንትና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሜዬ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
1K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopian News Agency

21.3K
Ethiopian News Agency official telegram channel
Открыть в Telegram