የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ምዝገባ የሚያከናወኑበትን ጊዜ እስከ የካቲት 16፤ 2018 አራዘመ። ቦርዱ የምዝገባ ጊዜውን ያራዘመው፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቋሙ ባዘጋጃቸው የተለያዩ መድረኮች ላይ እና በጽሁፍ ጭምር ባቀረቡት ጥያቄ መሆኑን አስታውቋል።
ምርጫ ቦርድ ባለፈው ህዳር ወር መጨረሻ ይፋ ባደረገው የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ፤ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወነው ከጥር 1 እስከ የካቲት 1 ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነበር። በዚህ መሰረት ምዝገባው የሚጠናቀቀው ከነገ በስቲያ እሁድ ቢሆንም፤ ቦርዱ ዛሬ አርብ ጥር 29 ምሽት ባወጣው መግለጫ ለዕጩዎች የተሰጠው ጊዜ በሁለት ሳምንት መራዘሙን አመልክቷል።
ቦርዱ በዛሬው መግለጫው፤ ከዚህ ወር መጀመሪያ አንስቶ ሲካሄድ በቆየው የዕጩዎች ምዝገባ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል፤ 15 የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ በሁለት የተለያዩ ቅንጅቶች እና በአንድ ግንባር ስር ሆነው ተወዳዳሪዎችን ማስመዘገባቸውን ገልጿል። የግል ዕጩዎችም በተመሳሳይ መልኩ ምዝገባ እያከናወኑ መሆኑንም ጠቁሟል።
የዕጩዎቹ ምዝገባ ሲከናወን የቆየው፤ ቦርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ባደረገው የዲጂታል ምዝገባ ስርዓት ነው። ባለፈው ታህሳስ ወር መጨረሻ ይፋ ይተደረገው ይህ ስርዓት “ለአካታችነት” እና “ተደራሽነት” ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ “የዕጩዎችን እና የመራጮችን ጊዜ እንደሚቆጥብ”፤ “አላስፈላጊ ምልልሶችን እንደሚያስቀር” እና “ወጪ ቆጣቢ” እንደሆነ ምርጫ ቦርዱ በወቅቱ አስታውቆ ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴ለዝርዝሩ ➡️
https://ethiopiainsider.com/2026/17332/
@EthiopiaInsiderNews
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram