avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
02.01.2026 18:42
የአማራ ክልልን እና የፌዴራል መንግሥታትን በኃይል ለማስወገድ ተንቀሳቅሰዋል በሚል የሽብር ወንጀል ክስ ከተመሰረተባቸው ግለሰቦች መካከል ሶስቱ በዋስትና መለቀቃቸውን የተከሳሾቹ ጠበቃ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ።

እያንዳንዳቸው 200 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ ከተለቀቁት ተከሳሾች ውስጥ የኢዴፓ ከፍተኛ አመራር እና የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ አብዱራህማን አህመዲን እንደሚገኙበት ጠበቃው ገልጸዋል።

የፌደራል ዐቃቤ ሕግ አቶ አብዱራህማንን ጨምሮ በ23 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ የመሰረተው በሰኔ 2016 ዓ.ም ነበር። ለእስር ከተዳረጉ ሁለት ዓመት ሊሞላቸው ከሶስት ወራት ያነሰ ጊዜ የሚቀራቸው ተከሳሾቹ፤ በቀረበባቸውን የሽብር ክስ ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲከራከሩ ቆይተዋል።

ክሱን ሲመለከት የቆየው የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት፤ ዐቃቤ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ባለፈው ጥቅምት ወር መጨረሻ ትዕዛዝ መስጠቱን የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል።

ክሱ ተሻሽሎ ከቀረበ በኋላ፤ በከሳሽ እና በተከሳሾች መካከል ባለፈው ህዳር ወር አጋማሽ የዋስትና ክርክር መደረጉን ጠበቃው አስረድተዋል።

የግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው ችሎት፤ ዐቃቤ ሕግ ባሻሻለው ክስ ላይ የጠቀሰው የጸረ – ሽብር ድንጋጌ የዋስትና መብት የማያስከለክል በመሆኑ ክሳቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ለደንበኞቻቸው ዋስትና መፍቀዱንም አክለዋል።

ተከሳሾቹ በፍርድ ቤት እንዲያሲዙ የተላለፈባቸውን የ200 ሺህ ብር ዋስትና በመክፈል፤ በዚያኑ ዕለት ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተለቅቀው እንደነበር አቶ ሰለሞን ተናግረዋል።

🔴ለዝርዝሩ➡️ https://ethiopiainsider.com/2024/13273/

@EthiopiaInsiderNews
10
🤔 2
👏 1
4 6.1K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram