avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
11.11.2025 19:19
የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በአንድ ወር ገደማ ለሁለተኛ ጊዜ በጠራው አስቸኳይ ጉባኤ፤ የከተማይቱን አዲስ ከንቲባ ሹመት እንደሚያጸድቅ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ።

ምክር ቤቱ በነገው ዕለት በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባኤው ሹመታቸው የሚጸድቅላቸው፤ ከአምስት ዓመት በፊት የከተማይቱ ከንቲባ የነበሩት አቶ ጥራቱ በየነ መሆናቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

የከተማይቱ ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ ህዳር 2፤ 2018 ለአባላቱ ባስተላለፈው ጥሪ፤ በነገው ዕለት አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚካሄድ አረጋግጧል። ምክር ቤት በዚሁ ጥሪው፤ አባላቱ ነገ ጠዋት በሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት በሚገኘው አዳራሽ እንዲገኙ ቢያሳስብም የጉባኤውን አጀንዳ ግን ከመግለጽ ተቆጥቧል።

የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት ባለፈው ጥቅምት ወር መጀመሪያ በተመሳሳይ መልኩ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ፤ ከተማይቱን በከንቲባነት እንዲመሩ የተሾሙትን የአቶ ተክሌ ጆንባን ሹመት አጽድቆ ነበር።

የሲዳማ ክልል የእንስሳት ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ተክሌ፤ በዚህ የኃላፊነት ቦታቸው ላይ አንድ ወር ያህል ጊዜ እንኳ ሳይቆዩ ወደ ፌደራል ተቋም ተዘዋውረዋል መባሉ የሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።

ለዚህ መነሻ የሆነው፤ አቶ ተክሌ ከጥቅምት 21፤ 2018 ጀምሮ የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨቱ ነበር።

ይህ ደብዳቤ በአድራሻቸው እንዳልደረሳቸው አቶ ተክሌ ባለፈው እሁድ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስታውቀው ነበር።  የእንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ለአቶ ተክሌ የተጻፈ እና በእጃቸው የሚሰጥ ደብዳቤ ለመስሪያ ቤቱ መድረሱን አረጋግጠዋል።

🔴ለዝርዝሩ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16625/

@EthiopiaInsiderNews
6
👍 4
👏 2
👎 1
7 7.4K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram