avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
24.10.2025 12:48
ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ሶስት ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ ካገኘችው 2.5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የያዙት ወርቅ፣ ቡና እና አበባ መሆናቸውን የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ተናገሩ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ሀገሪቱ ከወርቅ ሽያጭ ብቻ ያገኘችው ገቢ 1.2 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

ዶ/ር ፍጹም ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ጥቅምት 12፤ 2018 በተካሄደው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የመቶ ቀናት እቅድ ግምገማ ላይ ባቀረቡት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም ሪፖርት ነው። የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ በዚሁ ሪፖርታቸው፤ መንግስት ባለፉት ሶስት ወራት ወደ ውጪ ከሚላኩ ሸቀጦች ለማግኘት አቅዶ ከነበረው ገቢ “ከመቶ ፐርሰንት በላይ” ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከዚህ ዘርፍ ለማግኘት አቅዳ የነበረው የገንዘብ መጠን 2.1 ቢሊዮን ዶላር ነበር። ከእቅድ በላይ 117 በመቶ ስኬት የተመዘገበበት እንደሆነ በተገለጸው የወጪ ንግድ ዘርፍ ከፍተኛውን የገቢ ድርሻ የያዙት ወርቅ እና ቡና ናቸው።

ኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ወራት ከወርቅ ያገኘችው የገቢ መጠን 1.2 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ለፌደራል መንግስት ካቢኔ አባላት ተናግረዋል። ይህ የገቢ መጠን መንግስት በእቅድ ከያዘው 135.7 በመቶውን ያሳካ እንደሆነም በሪፖርታቸው አመልክተዋል።

🔴ለዝርዝሩ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16497/

@EthiopiaInsiderNews
18
🔥 1
3 8.9K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram