avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
15.10.2025 18:59
ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ሶስት ወራት ብቻ ወደ ውጭ ከላከቻቸው ምርቶቿ 2.48 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ። በዚሁ ሩብ ዓመት ሚኒስቴሩ የሚከታተላቸው እንደ ጥራጥሬ እና የቅባት እህሎች ከመሳሰሉ ምርቶች 149 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱንም መስሪያ ቤቱ ገልጿል።

ሚኒስቴር ይህን የገለጸው፤ የ2018 በጀት ዓመት የሶስት ወራት እቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ ከመስሪያ ቤቱ እና ከተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ላይ ነው። ከውይይቱ መጠናቀቅ በኋላ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ አቶ ካሳሁን ጎፌ በሰጡት መግለጫ፤ በወጪ ንግድ ረገድ በሩብ ዓመቱ ከተያዘው እቅድ “117 ፐርሰንት” መፈጸም መቻሉን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ (export) በጠቅላላ ለማግኘት ያቀደችው ገቢ 9.4 ቢሊዮን ዶላር ነው። ሀገሪቱ ባለፈው በጀት ዓመት ከዚሁ ዘርፍ ያገኘችው ገቢ 8.3 ቢሊዮን ዶላር እንደነበር መገለጹ ይታወሳል። ይህ የገቢ መጠን በሀገሪቱ ታሪክ “ለመጀመሪያ ጊዜ” የተመዘገበ መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከሳምንት በፊት ፓርላማውን በከፈቱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ላይ አስታውቀው ነበር።

በዘንድሮው በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ገቢ ካለፈው ዓመት በ1.1 ቢሊዮን ዶላር የላቀ ነው። በዘርፉ ባለፉት ሶስት ወራት የተመዘገበው የገቢ መጠን፤ ይህንን እቅድ ማሳካት እንደሚቻል “ከወዲሁ አመላካች ሆኗል” ብለዋል አቶ ካሳሁን በትላንቱ መግለጫቸው።

🔴ለሙሉ ዘገባው ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16436/

@EthiopiaInsiderNews
4
🥰 2
😁 2
💩 1
7 8.2K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram