avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
12.10.2025 19:11
በአፋር ክልል፣ ኪልበቲ ረሱ ዞን፣ በርሃሌ ወረዳ ትላንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ 43,456 ሰዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ሁሴን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። ለተፈናቃዮቹ የሚሆን ምግብ እና መጠለያ፤ ከባድ ጉዳት ወደ ደረሰባቸው ቀበሌዎች እየተጓጓዘ መሆኑንም ገልጸዋል። 

በክልሉ ትላንት ቅዳሜ ጥቅምት 1፤ 2018 ምሽቱ የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ከበርሃሌ በተጨማሪ በተመሳሳይ ዞን ውስጥ በሚገኙት ኮናባ እና ዳሎል ወረዳዎችም የተከሰተ እንደነበር የአፋር ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። በበርሃሌ ወረዳ የመጀመሪያው ርዕደ መሬት ከደረሰበት ከትላንት ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ ለስድስት ጊዜያት ያህል የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን አቶ አሊ አስረድተዋል።

በወረዳው ካሉ ቀበሌዎች በርዕደ መሬቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው፤ ቡሬ እና አስ ጉቢ አላ ቀበሌዎች መሆናቸውን ዋናው አስተዳዳሪው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በአደጋው ሳቢያ በቀበሌዎቹ ነዋሪ የሆኑ ስድስት ሰዎች መጎዳታቸውን እንዲሁም አንድ የ12 ዓመት አዳጊ ልጅ ህይወት ማለፉንም ገልጸዋል።

ከተጎጂዎቹ ውስጥ ሶስቱ ወደ በርሃሌ ሪፈራል ሆስፒታል ተወስደው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን አቶ አሊ አመልክተዋል። በሁለቱ ቀበሌዎች የቤቶች መፍረስን ያስከተለው ርዕደ መሬት በተከሰተበት ወቅት አብዛኞቹ ነዋሪዎች ከቤት ውጭ የነበሩ በመሆኑ የተጎጂዎች ቁጥር ሊቀንስ መቻሉንም አብራርተዋል።

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16367/

@EthiopiaInsiderNews
😭 10
6
👏 2
😁 1
💔 1
15 7.2K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram