avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
01.07.2025 19:06
የመንግስት ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” ማሳደግ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ  

የፌደራል መንግስት የሚሰብሰበውን ገቢ በሚቀጥለው ዓመት “በከፍተኛ ደረጃ” ለማሳደግ ማቀዱ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ያለውን የልማት ፍላጎት ከአሁን በኋላ ማሳካት የሚቻለው ገቢን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ፤ “አዲስ የልማት ጥያቄ ለመፍታት ብለን ከብሔራዊ ባንክ የምንበደርበት ሁኔታ አብቅቶለታል” ብለዋል። 

የገንዘብ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። የዛሬው መደበኛ ስብሰባ ዋነኛ ትኩረቱን ያደረገው፤ የፌደራል መንግስት ለ2018 ባዘጋጀው በጀት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ነበር። 

የፌደራል መንግስት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለፓርላማ ያቀረበው የበጀት መጠን 1.93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን ከሀገር ውስጥ ምንጮች ለመሰብሰብ ያቀደው የገንዘብ መጠን 1.23 ትሪሊዮን ብር ነው። በቀጣዩ በጀት ዓመት ከታክስ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው 1.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ፤ ለዘንድሮ በእቅድ ከተያዘው በ200 ቢሊዮን ብር ገደማ ጭማሪ አለው።

የ2018 በጀትን አስመልክቶ በዛሬው የፓርላማ ውይይት ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ፤ የፌደራል መንግስት የሀገር ውስጥ ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” የማሳደግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት በአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ የሚያገኘውን የገቢ መጠን በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍ የማድረግ እቅድ እንዳለውም ጠቁመዋል።

🔴ለዝርዝሩ:- https://ethiopiainsider.com/2025/16204/

@EthiopiaInsiderNews
21
👎 18
👍 4
🤔 1
19 11.6K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram