avatar
Ethiopia Insider
Переслано от канала
26.03.2026 15:28
ኢዜማ በ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘገባ የተሰማውን ቅሬታ አቀረበ

“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትላንት ሐሙስ፣ መጋቢት 16፤ “ገዢው ፓርቲ የኢዜማ መሪና ምክትላቸው ለፓርላማ በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ” በሚል ርዕስ ለንባብ ላበቃው ዜና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰማውን ቅሬታ ለዝግጅት ክፍሉ በደብዳቤ አድርሷል።

ኢዜማ ዘገባውን “በተሳሳተና የጋዜጠኝነት ስነምግባርን ባልተከተለ መልኩ አንባቢያን የተሳሳተ ግምት እንዲወስዱ በሚያደርግ” መንገድ ተዘጋጅቷል ያለ ሲሆን፣ ሚዲያው “በፓርቲው ላይ የያዘውን የተዛባ አቋም በግልፅ የሚያሳይ እና ከአንድ ለእውነት እቆማለሁ ብሎ ከተነሳ ሚዲያ የማይጠበቅ እንዲሁም የጋዜጠኝነትን ስነምግባር ያልተከተለ ዘገባ ከፍተኛ ቅሬታ ተሰምቶናል።” ብሏል።

ሙሉውን የፓርቲውን የቅሬታ ድብዳቤ እዚህ ያንብቡ፤ https://ethioelections.com/2026/03/17436/
😁 15
5
👎 2
3 5.2K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram