avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
19.03.2026 16:57
ፓርላማው “ምልዓተ ጉባኤ ማሟላት” ባለመቻሉ መደበኛ ስብሰባውን ሳያካሄድ ቀረ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ሊያካሄደው የነበረውን መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አባላት ምልዓተ ጉባኤ ሳይሟላ በመቅረቱ ለመሰረዝ ተገደደ። ምክር ቤቱ ውሳኔውን ከማስተላለፉ አስቀድሞ፤ የፓርላማው ሰራተኞች “ዝግ ስብሰባ” እንደሚደረግ በመግለጽ ጋዜጠኞች ከስብሰባ አዳራሽ እንዲወጡ አድርገዋል።

መደበኛ ስብሰባዎቹን ዘወትር ማክሰኞ እና ሐሙስ የሚያካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ለዛሬ መጋቢት 10፤ 2018 በስድስት ጉዳዮች ላይ ለመወያየት አጀንዳ ይዞ ነበር። ከአጀንዳዎቹ አራቱ የኢትዮጵያ መንግስት ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያደረጋቸውን የብድር ስምምነቶች የሚመለከቱ ናቸው።

ፓርላማው በዛሬው ስብሰባው በአጀንዳነት የያዘው ሌላው ጉዳይ፤ ላለፉት 12 ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያን ተመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መምራት ነበር። ሆኖም ከዚህ ቀደም እምብዛም ባልተለመደ መልኩ፤ ፓርላማው “ምልዐተ ጉባኤ አልተሟላም” በሚል ምክንያት መደበኛ ስብሰባውን ሳያካሄድ ቀርቷል።

“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያነጋገረቻቸው አራት የፓርላማ አባላት፤ ይኸው ምክንያት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች በኩል እንደተነገራቸው ገልጸዋል። ምልዓተ ጉባኤው ካልተሟላባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ለእረፍት ወደ ምርጫ ክልላቸው የሄዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በጊዜ ባለመመለሳቸው መሆኑን ከጽህፈት ቤቱ እንደተረዱ የፓርላማ አባላቱ ተናግረዋል።

🔴ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2026/17688/

@EthiopiaInsiderNews
9
👍 5
😁 4
🤔 1
8 7.4K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram