“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) ከጥር 16 እስከ የካቲት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ባለው የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በምሽት ሁለት ሰዓት ዜናዎቹ ያቀረባቸውን የቅድመ ምርጫ ዘገባዎች የተመለከተ ዳሰሳ አካሄዷል። በዚህም መሰረት በመንግሥት በጀት የሚተዳደረው ይህ መገናኛ ብዙኃን ለሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ተመጣጣኝ እና ፍትሓዊ የዘገባ ሽፋን እንዳልሰጠ ማረጋገጥ ችሏል።
በዳሰሳው መሠረት ብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ የአየር ሰዓት ከተሰጣቸው አምስት ዘገባዎች ውስጥ ሁለቱን አግኝቷል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በብልፅግና ፓርቲ ስብሰባ ላይ ምርጫን በተመለከተ ያቀረቡት ንግግር ላይ ያተኮረ ዜና ብቻውን 10 ደቂቃ በመውሰድ ከፍተኛ የአየር ሰዓት ሽፋን ሲያገኝ፣ ለፓርቲው ማኒፌስቶ እና አርማ ማስተዋወቂያ የተዘጋጀው ፕሮግራም ደግሞ 4 ደቂቃ ከ10 ሰከንድ በመውሰድ አራተኛ ከፍተኛ የአየር ሰዓት ሽፋን አግኝቷል።
በአንፃሩ “የመገናኛ ብዙኃንና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ ሥነ-ምግባር እና አሠራር መመሪያ ቁጥር 02/2013” በአንቀጽ 16(1) ላይ የመንግሥት ሚዲያዎች “ሁሉም ተወዳዳሪ ፓርቲዎች አቋማቸውን ለመራጭ ሕዝቡ ለማቅረብ ፍትሓዊ ዕድል እንዲያገኙ” የማድረግ ግዴታ ጥሎባቸዋል። እንዲሁም በአንቀጽ 16(6) መሠረት በምርጫ ወቅት ለሚዘጋጁ የውይይት፣ የክርክር እና የቃለ-መጠይቅ ፕሮግራሞች ተገቢ የዜና ሽፋን መስጠት እንዳለባቸው ይደነግጋል።
ሙሉ የዳሰሳውን ውጤት የሚመለከተውን ዘገባ እዚህ ያንብቡ:-
https://ethioelections.com/የኢትዮጵያ-ቴሌቪዥን-የቅድመ-ምርጫ-2018-አዘጋ/
#ምርጫ2018 #EthiopiaElection #EBCNews
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram