avatar
Ethiopia Insider
@EthiopiaInsiderNews
11.03.2026 18:26
በጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ ሳቢያ የ63 ሰዎች ደብዛ ጠፋ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች በተከሰተ የመሬት ናዳ 35 ሰዎች ሲሞቱ፤ የ63 ሰዎች ደብዛ መጥፋቱን የዞኑ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በመሬት ናዳው ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከፍ ሊል እንደሚችልም ጽህፈት ቤቱ ስጋቱን ገልጿል።

የመሬት ናዳው የተከሰተው፤ በጋሞ ዞን ደጋማ አካባቢዎች ከትላንት ማክሰኞ መጋቢት 1፤ 2018 በጣለ “ከባድ ዝናብ” ምክንያት እንደሆነ የዞኑ አስተዳደር ትላንት ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቆ ነበር። የዞኑ አስተዳደር ዛሬ ባሰራጨው መረጃ፤ በጎርፍ እና በመሬት ናዳ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 35 መድረሱን አመልክቷል።

በዞኑ ስር የሚገኘው የጋጮ ባባ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዛሬ ጠዋት በፌስቡክ ገጹ ባጋራው መረጃ፤ ማዞ ዶይሳ እና ላካ በተባሉ ቀበሌዎች በደረሰ የመሬት ናዳ በአጠቃላይ የ96 ሰዎች ደብዛ መጥፋቱን ገልጿል። የመሬት ናዳው ሰለባ ከሆኑት መካከል “የሰላሳ ሶስቱ አስክሬን መገኘቱንም” የገለጸው ጽህፈት ቤቱ፤ የሟቾቹን አስከሬን የማፈላለግ ስራው መቀጠሉንም አስታውቋል።

የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ማኑቆ፤ በወረዳ በኩል የተገለጸውን የሟቾች ብዛት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል። ከተለያዩ ወረዳዎች መረጃዎች ለጽህፈት ቤታቸው እየደረሱ መሆኑንም የተናገሩት ኃላፊው፤ በጋጮ ባባ ወረዳ በኩል የተገለጸው “የተጠቃለለ መረጃ” እንዳልሆነ አስረድተዋል።

🔴ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2026/17650/

@EthiopiaInsiderNews
😭 11
5
😢 2
👍 1
7 7.3K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Ethiopia Insider

17.5K
Ethiopia Insider is a digital media that provides news, updates, analysis and features.
Открыть в Telegram