Dashen Bank @DashenBankEthiopia 18.03.2026 15:37 Скопировать Пожаловаться ዳሸን ባንክ በደሴና በወላይታ ሶዶ ከተሞች ከደንበኞቹ ጋር የኢፍጣር ፕሮግራም አካሄደ የተከበረውን የረመዳን ወር በማስመልከት ዳሸን ባንክ በደሴና በወላይታ ሶዶ ከተሞች ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት (ሸሪክ) ደንበኞቹ ጋር የኢፍጣር ፕሮግራም አካሂዷል። ይህ ፕሮግራም የረመዳን ወር መንፈሳዊ እሴቶችን ለማጠናከር፣ አንድነትን ለማጎልበት እንዲሁም ባንኩ ከደንበኞቹ ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት ለማጠናከር ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ መርሃ-ግብር ነው። የእለቱ ታዳሚዎች በተዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም ደስታቸውን በመግለጽ፣ እንዲህ ባለ መልኩ በአብሮነት ኢፍጣር ማካሄድ በእምነቱ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ለባንኩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ❤ 20 👍 2 1 2 8.8K
Обсуждение 1
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram