Dashen Bank @DashenBankEthiopia 18.03.2026 13:21 Скопировать Пожаловаться ዳሸን ባንክ ከባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በድርጅቱ የኢፍጧር መርሃ-ግብር አዘጋጀ የዳሸን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት "ሸሪክ" በባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት የኢፍጣር መርሃ-ግብር አዘጋጅቷል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የባንኩ የስራ ኃላፊዎች ዳሸን ባንክ ሸሪክ በታላቁ የረመዳን ወር ተቋሙ ድረስ የመጣው አጋርነቱን ለማሳየት እንደሆነ ገልጸው ፤ ባንኩ በቀጣይም ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ይሰራል ብለዋል። የባቡል ኸይር የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሐናን አህመድ በበኩላቸው ድርጅቱ በረመዳን ወር ብቻ 7 ሺህ የሚደርሱ አቅመ ደካሞችን እያስፈጠረ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ባቡል ኸይር በርካታ አቅመ ደካማ እናቶችን፣ ህጻናትና ሴቶችን ከምገባ ጀምሮ ፣ የሙያ ክህሎት እንዲኖራቸው እና ራሳቸውን እንዲችሉ እየሰራ ነው ብለዋል። በተጨማሪም አቅመ ደካሞች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እየሰራ እንደሆነም ገልጸዋል። በበጎ አድርጎት ድርጅቱ በቋሚነት የሚደገፉ የአቅመ ደካሞች ቁጥር ከ5ሺ በላይ እንደሆኑም ተናግረዋል። ❤ 20 👍 1 2 7.8K
Обсуждение 2
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram