Dashen Bank @DashenBankEthiopia 17.03.2026 14:36 Скопировать Пожаловаться ዳሸን ባንክ በነቀምቴ እና በወራቤ ከተሞች የሰደቃ መርሃ-ግብር አካሄደ ዳሸን ባንክ የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ “ለእናቴ” በሚል መሪ ቃል በነቀምቴ እና በወራቤ ከተሞች ለአቅመ ደካሞች የሰደቃ መርሃ-ግብር አካሂዷል። በመርሃ-ግብሩ በሁለቱ ከተሞች ሐሚገኙ እናቶች የዘይት፣ የዱቄት እና የቴምር ድጋፍ ተደርጓል ። ድጋፉ የተደረገላቸው እናቶች ባንኩ ላደረገላቸው ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን ገልጸዋል። ዳሸን ባንክ ከመደበኛ የባንኪንግ አገልግሎቱ በተጨማሪም ማህበራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት በርካታ ተግባራትን እየከናወነ ሲሆን ይህ ድጋፍም ከእነዚህ አንዱ ሲሆን መሰል መርሃ-ግብሮችን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም እየተካሄደ ይገኛል። ❤ 17 👍 1 2 8.7K
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram