Bunna Bank @BunnaBankOfficial 09.03.2026 16:16 Скопировать Пожаловаться ቡና ባንክ በባህር ዳር ለሚገኙ ወገኖች የሰደቃ ድጋፍ አደረገ የቡና ባንክ ባህር ዳር ዲስትሪክት ታላቁን የረመዷን ወር ምክንያት በማድረግ፣ በዲስትሪክቱ ዙሪያ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች የሰደቃ (የድጋፍ) መርሃ ግብር አካሄደ። ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለው ቁርጠኝነት መሰረት፣ የዲስትሪክቱ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ አበርክቷል። ይህም ድጋፍ ነዋሪዎቹ የረመዷንን ወር በደስታና በሰላም እንዲያሳልፉ ለማገዝ የታለመ ነው። ቡና ባንክ ከንግድ ስራው ጎን ለጎን ለማህበረሰቡ ደህንነት ትልቅ ቦታ የሚሰጥ ባንክ እንደመሆኑ፤ ይህ የሰደቃ ስነስርዓትም እንደሁልጊዜው ሁሉ ከህዝባችን ጋር ያለንን አጋርነት የምናሳይበት ነው ሲል ዲስትሪክቱ አስታውቋል። የባለራዕዮች ባንክ የሆነው ቡና ባንክ ማህበረሰቡን የሚያሳትፉ መሰል በጎ ተግባራትን አቅም በፈቀደ መጠን ማከናወኑን አጠናክሮ ይቀጥላል። ቡና ባንክ - የባለራዕዮች ባንክ! #ቡናባንክ #ረመዷን_ከሪም #ባህርዳር #ሰደቃ #ኢትዮጵያ #BunnaBank #BahirDar #Ramadan2026 ❤ 41 👏 15 😁 6 6 4 9.7K
Обсуждение 6
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram