avatar
Amhara Media Corporation
@AmharaMassMedia
07.04.2026 15:12
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ።
ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት በኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የማይረሳ እና ታላቅ ዐሻራን ማሳረፍ የቻሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ተሰምቶኛል ብለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት እስከ ከፍተኛ ዲፕሎማትነት በደረሰ ረጅም የሥራ ዘመናቸው ለሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያስመዘገቡት ድል እና ያበረከቱት አስተዋጽዖ ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው።
አምባሳደር ቆንጂት ለኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከነበራቸው አበርክቶ ባለፈ ለሴት ዲፕሎማቶችም የጽናት እና የጥንካሬ ተምሳሌት ነበሩ ነው ያሉት።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑር፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ ብለዋል በመልዕክታቸው።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
������
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
3
1 2.3K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Amhara Media Corporation

48.7K
አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
Открыть в Telegram