avatar
Amhara Media Corporation
@AmharaMassMedia
07.04.2026 12:29
አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ባሕር ዳር: መጋቢት 29/2018 ዓ.ም (አሚኮ)አንጋፋዋ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አምባሳደር ቆንጂት የውጭ ጉዳይ ሚንስቴርን በ1950ዎቹ በለጋ እድሜያቸው እንደተቀላቀሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። አምባሳደሯ ከዴስክ ኦፊሰርነት እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል።
አምባሳደር ቆንጂት ከዮዲት እምሩ በመቀጠል በኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሴት አምባሳደርም ናቸው።
አምባሳደሯ በኦቶዋ፣ ካይሮ፣ ቴል አቪቭ እና ቬይና በሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኾነው አገልግለዋል።
በአፍሪካ ኅብረት እና በተባባሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽንም ቋሚ መልዕክተኛ በመኾን ሠርተዋል።
ከሰኔ 2009 እስከ መስከረም 2011ዓ.ም ደግሞ ኢጋድ በመራው የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ላይም ልዩ አማካሪ ነበሩ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአምባሳደር ቆንጂት ሕልፈት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
������
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
9
2.5K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Amhara Media Corporation

48.7K
አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
Открыть в Telegram