በህገወጥ የነዳጅ ግብይት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገለጸ።
በነዳጅ ስርጭትና ግብይት ሂደት ላይ የሚታዩ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር በስድስት ክልሎችና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች የተጀመረው የተቀናጀ ዘመቻ መጠነ ሰፊ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር አስታውቋል፡፡
በሕገ-ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ 250ሺህ 221 ሊትር ቤንዚን እና 198 ሺህ 432 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል ብለዋል፡፡
እንዲሁም በህገወጥ ድርጊቱ ተሳትፎ የነበራቸው 613 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥሩ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል፡፡
ዝርዝሩን ለመከታተል ሊንኩን ይጫኑ��
https://youtu.be/dGb6A6tWKyc
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram