Abay Bank @abaybanksharecompany 07.04.2026 16:40 Скопировать Пожаловаться ዓባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ጋር የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ ------------------------- ዓባይ ባንክ ከኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ጋር በስትራቴጂያዊ የቢዝነስ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሥምምነት በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል። የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እና የኢትዮጵያ አይ ቲ ፓርክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ በለጠ እሱባለው የመግባቢያ ሥምምነቱን ተፈራርመዋል፡፡ ኃፊዎቹ ለሁለቱ ተቋሞች ብቻ ሳይሆን ለአገር ዕድገት በሚጠቅሙ ቁልፍ የፋይናንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ በመርሐ-ግብሩ ተናግረዋል። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የማኔጅመንት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ ዓባይ - የታላቅነት ምንጭ! 👍 21 ❤ 14 🤩 3 👏 1 10 5K
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram