24.02.2026 20:41
ውድ ደንበኞቻችን፣

በኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ አዋጅ ቁጥር 1386/2025 እና በደንብ ቁጥር 576/2025 መሰረት፣ ከየካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም ባንኮች እና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ከደንበኞች ላይ ክፍያዎችን በመሰብሰብ በብሔራዊ ባንከ በተያዘው የኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ጽ/ቤት ሒሳብ ገቢ እንዲያደርጉ ተደንግጓል፡፡ 

በመሆኑም ባንካችን ከሚሰጠው ማንኛውም ዓይነት መደበኛ ብድር ላይ የሚለቀቀውን መጠን 1 በመቶ፣ እንዲሁም በሁሉም የባንካችን የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቶች ደንበኞች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ ላይ 5 በመቶ እየተጨመረ የሚሰበስብ እና ለኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ ጽ/ቤት ገቢ የሚያደርግ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡  

ለተጨማሪ መረጃ በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ ወይም ወደ 8834 የደንበኞች አገልግሎት የጥሪ ማዕከል መደወል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን። 

ዓባይ - የታላቅነት ምንጭ!
12
👍 1
17 7.3K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Abay Bank

26.8K
Vision:
To Become the First Bank of Choice

Mission:
Providing the best- in-class banking services and adding value for stakeholders

Core Values:
Customer - Centricity
Accountability
Teamwork
Employee - Centricity
Innovation
Открыть в Telegram