avatar
Bank of Abyssinia
@BoAEth
31.03.2026 14:59
ባንካችን አቢሲንያ በጅማ ከተማ በአብዱልከሪም አባገሮ (ፔሌ) ስም አዲስ ቅርንጫፍ ከፈተ

የባንካችን ጅማ ዲስትሪክት መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአቶ አብዱልከሪም አባገሮ (ፔሌ) ስም በጅማ ከተማ በተለምዶ ፈረንጅ አራዳ አካባቢ እጅግ ዘመናዊ ቅርንጫፍ ከፈተ።

ቅርንጫፎቹን በሃገር ባለውለታዎች በመሰየም የሚታወቀው ባንካችን ከዚህ ቀደም የጅማ ከተማ ቆርቋሪ በሆኑት በንጉሥ አባጅፋር ስም ቅርንጫፍ የከፈተ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ የሳቸዉ አራተኛ ትውልድ በሆኑት  አብዱልከሪም አባገሮ (ፔሌ) በከተማዋ 10ኛ ቅርንጫፉን ከፍቷል።

በ1952 ዓ.ም በጅማ ከተማ የተወለዱት አብዱልከሪም አባገሮ በኢትዮጵያ ተስፋ ብሔራዊ ቡድን ውስጥ በመጫወት ስማቸው በጉልህ የሚወሳ ሲሆን፣ “ፔሌ” የሚለውን የቅጽል ስም ያገኙትም በወቅቱ በነበራቸው ድንቅ የእግር ኳስ ብቃት ምክንያት ነበር። 

አቶ አብዱልከሪም የአምስቱ ጊቤ ታሪክ አባት በመባል ሲታወቁ፣ በተለይም የሰላም አምባሳደር ከመሆናቸዉ ጋር ተያይዞ ብዙዎች ''የጂማው ማህተመ ጋንዲ'' ሲሉ ይጠሯቸዋል።

አቶ አብዱልከሪም  በልማት፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በታሪክና ባህል ዘርፎች በርካታ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን በማከናወን ለጅማ ከተማ ብሎም ለሃገራቸው ጉልህ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የጅማ ከተማ የሰላም አምባሳደር በመሆን በተለያዩ ተቋማት በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

በመርሃ ግብሩ ላይም የጅማ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች፣ የባንካችን ከፍተኛ የሥራ ሐላፊዎች፣ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል።
37
👍 11
👏 5
🔥 3
🤔 2
😱 2
😁 1
1 14.8K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Bank of Abyssinia

186.2K
Bank of Abyssinia – The Choice for All
Welcome to BoA’s official Telegram channel!

Use @BOA_ATM_bot to access:

ATM locators
Card services & support
Real-time updates
Открыть в Telegram