avatar
Bank of Abyssinia
@BoAEth
13.03.2026 23:02
በዚህ በታላቁ የረመዳን ወር የበጎነት ተግባራት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጉልህ የሚስተዋሉበት ጊዜ እንደመሆኑ፣ ባንካችን እየከወነው የሚገኘው ከወገኖቻችን ጋር በአብሮነት የመቆምና የአስቤዛ የማቅረብ ተግባር በመቐለ ከተማ አካሂዷል ።

ለበጎነት የተዘረጉት የአቢሲንያ አሚን እጆች እንደ ሁልጊዜውም በፆም ወቅት በቂ ማፍጠሪያ ማግኘት ለማይችሉና ለተቸገሩ ወገኖቹ በመድረስ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በዚህም በከተማዋ ከሚገኘው ቀልም ፋውንዴሽን እና የትግራይ ሙስሊም ሴቶች ማህበር ጋር በመቀናጀት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ተወጥቷል። በፕሮግራሙ ላይም የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ዋና ጸሐፊ ሀጅ መሀመድ ካህሳይ፣ የቀልም ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አሚራ ሙስጠፋ፣ የትግራይ ሙስሊም ሴቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ናስራ አህመድ እንዲሁም የመቐለ ዲስትሪክት አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተከናውኗል።

ባንካችንም ከመቼውም ጊዜ በላይ የበጎነት አሻራውን በማሳረፍ ከተቸገሩ ወገኖቹ ጎን እንደሚቆም አስመስክሯል።

አሚን ለበጎነት!
64
👍 13
😱 4
🔥 3
4 17.3K

Обсуждение 0

Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.

Обсудить в Telegram

Bank of Abyssinia

186.2K
Bank of Abyssinia – The Choice for All
Welcome to BoA’s official Telegram channel!

Use @BOA_ATM_bot to access:

ATM locators
Card services & support
Real-time updates
Открыть в Telegram