Bank of Abyssinia @BoAEth 13.03.2026 23:02 Скопировать Пожаловаться በዚህ በታላቁ የረመዳን ወር የበጎነት ተግባራት ከመቼውም ጊዜ በላይ በጉልህ የሚስተዋሉበት ጊዜ እንደመሆኑ፣ ባንካችን እየከወነው የሚገኘው ከወገኖቻችን ጋር በአብሮነት የመቆምና የአስቤዛ የማቅረብ ተግባር በመቐለ ከተማ አካሂዷል ። ለበጎነት የተዘረጉት የአቢሲንያ አሚን እጆች እንደ ሁልጊዜውም በፆም ወቅት በቂ ማፍጠሪያ ማግኘት ለማይችሉና ለተቸገሩ ወገኖቹ በመድረስ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በዚህም በከተማዋ ከሚገኘው ቀልም ፋውንዴሽን እና የትግራይ ሙስሊም ሴቶች ማህበር ጋር በመቀናጀት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ተወጥቷል። በፕሮግራሙ ላይም የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ዋና ጸሐፊ ሀጅ መሀመድ ካህሳይ፣ የቀልም ፋውንዴሽን ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አሚራ ሙስጠፋ፣ የትግራይ ሙስሊም ሴቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ናስራ አህመድ እንዲሁም የመቐለ ዲስትሪክት አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት ተከናውኗል። ባንካችንም ከመቼውም ጊዜ በላይ የበጎነት አሻራውን በማሳረፍ ከተቸገሩ ወገኖቹ ጎን እንደሚቆም አስመስክሯል። አሚን ለበጎነት! ❤ 64 👍 13 😱 4 🔥 3 4 17.3K
Обсуждение 0
Обсуждение не доступно в веб-версии. Чтобы написать комментарий, перейдите в приложение Telegram.
Обсудить в Telegram