avatar
Ethio telecom
@ethio_telecom
05.04.2026 11:00
መልካም የእረፍት ቀን!


#Sunday
#StayConnected
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
31
👍 17
🙏 5
😁 4
😡 2
29 7.4K
avatar
Ethio telecom
@ethio_telecom
04.04.2026 21:03
ኢትዮ ቴሌኮም የገባውን ቃል በተግባር በማረጋገጥ ለደንበኞቹ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በሽልማት አበረከተ!

ኢትዮ ቴሌኮም 130ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከመስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለደንበኞቹ ባዘጋጀው የኢትዮ 130 ሜጋ ፕሮሞ እና ኢትዮ 131 ላኪ ስሎት የሽልማት መርሃ ግብር ለዕድለኞች ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ሲያበረክት መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ክብረ በዓሉን ምክንያት በማድረግ እስካሁን 6 የኤሌክትሪክ መኪኖችን ለአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ጅማና ወሊሶ ባለዕድለኛ ደንበኞቻችን እንዲሁም 13 ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለአርባምንጭ፣ ሐረር፣ አርሲ ነጌሌ፣ አዲስ አበባ፣ ሆሳዕና፣ አዳማ፣ ሐዋሳ፣ ወልቂጤ እና ቦንጋ ዕድለኞች ቁልፍ ማስረከቡ ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም 422 ዘመናዊ ስማርት ስልኮችን፣ ለ4,405 ደንበኞቻችን በየቀኑ እና በየሳምንቱ በድምሩ 46 ሚሊዮን ብር የቴሌብር ኤሌክትሮኒክ ገንዘብ እንዲሁም ከ2.7 ሚሊዮን በላይ የሞባይል ጥቅሎችን ጨምሮ፣ ከ143 ሚሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ ዋጋ ያላቸውን ሽልማቶች አበርክቷል።

በትላንትናውና በዛሬው ዕለትም ዕጣ ለወጣላቸው የአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ጅማ እና የአሶሳ ባለዕድለኞች፣ ሦስት ዘመናዊ ቮልስዋገን (ID.4)፣ ሁለት የቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና አንድ ቶዮታ (BZ3x) የኤሌክትሪክ መኪኖችን የኩባንያችን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሚዲያ አጋሮቻችንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ቃል በገባው መሠረት በመሸለም ቁልፍ አስረክቧል፡፡

ኩባንያችን ደንበኞቹን ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ከመሸለም ባሻገር፣ ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ኢኒሼቲቭ ስኬትም የራሱን የላቀ ሚና በመወጣት ላይ ይገኛል።

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #RealizingDigitalEthiopia
53
👍 15
😡 7
😁 5
👏 2
🤣 1
39 4 10.3K
avatar
Ethio telecom
@ethio_telecom
04.04.2026 16:36
Ethio telecom Launches 4th Smart EV Charging Station in Adama.

#teleEvCharging #Adama
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
👍 25
16
😡 5
19 2 12.9K
avatar
Ethio telecom
@ethio_telecom
03.04.2026 23:42
ኩባንያችን አራተኛውን የህዝብ ኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ በአዳማ ይፋ አደረገ

ኩባንያችን ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ውጪ በአዳማ ከተማ ይፋ ያደረገው የህዝብ የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያ በአንድ ጊዜ 12 እጅግ በጣም ፈጣን መሙያዎችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም ያሉንን ጣቢያዎች የማስተናገድ አቅም በእጅጉ ከፍ ለማድረግ ያስችላል፡፡

ዋና ስራ አስፈጻሚያችን “ከአራቱ ጣቢያዎች በተጨማሪ ለተለያዩ ቁልፍ ሀገራዊ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ መሠረተ-ልማቶችን በመገንባት ላይ እንገኛለን ያሉ ሲሆን፣ ይህም የሀገራችን አረንጓዴ ልማት ሥነ-ምህዳርን ለመደገፍ ያለንን ጽኑ ቁርጠኝነት ያሳያል” ብለዋል፡፡

አክለውም “ሀገራችን ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ ዘላቂ የትራንስፖርት አማራጮች እና ዲጂታል ኢኖቬሽን የምታደርገውን ሽግግር እያፋጠነች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ እነዚህን የኤሌክትሪክ ኃይል መሙያ ጣቢያዎች በአጭር ጊዜ ገንብተን ስራ ላይ እንዲውሉ አድርገናል” ብለዋል፡፡

ኩባንያችን ቀደም ሲል በአንድ ጊዜ 48 መኪኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ጣቢያዎችን ወደ ስራ ያስገባ ሲሆን፣ ከየካቲት 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከ284 ሺህ በላይ የኤሌክትሪክ መኪኖች፣ 7,159,066.88 ኪሎዋት ኃይል መሙላት ችሏል፡፡

ይህም 10,028,363.32 ኪ.ግ ካርቦን ዳይኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ ማድረግ የቻለ ሲሆን፣ ከ49,559 በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር ይነጻጸራል።

በተጨማሪም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የገነቧቸው ጣቢያዎች በተቀናጀ የዲጂታል ስነ-ምህዳር ውስጥ እንዲካተቱ የሚያስችል ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ ፕላትፎርም ያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ተጠቃሚዎቻቸው ሁሉን አቀፍ የዲጂታል አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል፡፡

ለበለጠ መረጃ ፡ https://bit.ly/4mePALQ
55
👏 12
👍 10
😡 7
45 2 12.6K

Ethio telecom

311.1K
We Simplify lives & accelerate Ethiopia’s digital transformation & beyond via delivering reliable communications, innovative digital solutions & seamless financial services that empower communities, businesses & nations.

https://t.me/EthiotelecomChatBot
Открыть в Telegram